Kone Renaissance Foundation Logo

አላማና ራእይ

የፋውንዴሽናችን አላማ

በዚህ ትልቅ ትምህርት ቤት ውስጥ የሚያልፉትን የነገ ሃገር ተረካቢ ትውልድ ከሌላው አካባቢ ማህበረሰብ እንዲሁም በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በማስቻል የሚመጣው ትውልድ ሃላፊነት የሚሰማውና ብቁ ማድረግ ነው። ይህንንም ማድረግ እንድንችል በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ያሉ የአካባቢውን ተወላጆች እንዲሁም በትምህርት ቤቱ የተማሩ ቀደምት ተማሪዎችን በማስተባበር በትምህርት ቤቱ ውስጥ ያስፈልጋሉ ተብለው የሚታሰቡትን መሰረታዊ ፍላጎቶች በማቴሪያል መልክ መርዳትና ብሩህ ተስፋ ላላቸው ነገር ግን የአቅም ውስንነት ላለባቸው ተማሪዎችም የተለያየ ድጋፍ ማድረግ ነው።

ግብ

ትምህርት ቤቱን ከመደገፍ ባለፈ በተግባር የሚያምን ፣ ታታሪና አላማ ያለው ትውልድ መፍጠር!

KHSRF

የመጀመርያ ምስረታ

ፋውንዴሽናችን ሰኔ 20, 2017 አ.ም ተቋቋመ።

KHSRF

በ 2018/2025 የተያዘ እቅድ

የመማሪያ ቁሳቁስ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች ድጋፍ ማድረግና የዲጂታል ላይብረሪውን ኮምፒውተሮችን በመግዛት በትምህርት ቤቱ ውስጥ ባለው ቤተ-መጻሕፍት ውስጥ ራሱን የቻለ አንድ ሴክሽን ማድረግ ሲሆን የoffline አገልግሎት እንዲኖረው አስተማማኝ database መፍጠር ነው።

KHSRF

በቀጣይ 5 አመት የተያዘ እቅድ

ከፍተኛ ውጤት ላመጡና በትምህርት ቤቱ ውስጥ በመምህርነት ሞያ ለሚያገለግሉ መምህራን የስኮላርሽፕ እድልን ማፈላለግና የማማከር አገልግሎት፣ እንዲሁም የተጀመረውን የዲጂታል ላይብረሪ ፕላትፎርም በሃገር አቀፍ ደረጃ ተቀዳሚ የሃገር resource ማድረግ ነው።

KHSRF

ያሳካናቸው ግቦች

134 አጋዥ መጽሃፍትን የረዳን ሲሆን በዌብ ሳይታችንም የዲጂታል ላይብረሪ እና በአለም አቀፍ ደረጃ የሚሰጡ ነጻ የኦንላይን ትምህርቶችንና የስኮላርሽፕ እድሎችን እንዲሞክሩ በማካተት ለማህበረሰባችን አበርክተናል።

የዚህ ፋውንዴሽን መስራቾች

አቤል ቢሰጠኝ

አቤል ቢሰጠኝ

መስራች እና የትምህርት ቤቱ ተጠሪ

"በኮን 2ኛ ደረጃ ትም/ቤት ስም የተቋቋመው ፋውንዴሽን መነሻውም መድረሻውም በትምህርት ቤቱ ላሉ ማህበረሰብ (ተማሪዎች፣ መምህራን) አቅም በፈቀደ ላጋጠሙ ችግሮች መፍትሔ በመስጠት ከጊዜው ጋር ተወዳዳሪ ማድረግ ነው!"

ኮማንደር ወንድወሰን

ኮማንደር ወንድወሰን

መስራች እና ዳታ አናሊስት

"ይህ ፋውንዴሽን የኮን 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና ተማሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ፅኑ እምነት አለኝ። የዚህ ፋውንዴሽን አካል በመሆኔም ደስታ ይሰማኛል።"

ሰሎሞን ይመር

ሰሎሞን ይመር

መስራች እና የውጭ ግንኙነት

"በዚህ ፕሮጀክት ውስጤ ትልቅ እምነት አለው ፡ የዚህ በጎ ተግባር አካል መሆኔም በጣም ያኮራኛል።"

መንጥር ዘሩ

መንጥር ዘሩ

የአካባቢ ተወላጅና የፋውንዴሽኑ አባል

"አሁን ዓለም ላይ የማህበረሰብ ልማቶች የሚሰሩት በጋራ እና በትብብር ነው ። የተለያዩ ዕውቀቶች ፣ የሚሰበሰቡ ሀብቶች የሆነ ግልፅ አላማ ያለው ነገር ላይ ሲውሉ ታርጌት ይመታል ። የዚህ ዓይነት ትውልድ ላይ የሚሰሩ ስራዎች በኮሚትመንት ፣ በዕምነት ፣ በትጋት መሰራት አለባቸው ። ትልቅ ሀሳብና አላማ ይዞ በትንሽ ሰዎች ፣ በትንሺ ሀብት ተጀምሮ ተዓምረኛ ስኬት ላይ የደረሱ ድርጅቶች ብዙ ናቸው ። እንበርታ !"

የመስራቾቹ መልእክት

እንደ አንድ ቡድን፣ በኮን ሃይስኩል ለሚማሩ ወንድም እህቶቻችን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እና አስተምሮ እዚህ ደረጃ ያደረሰንን ትምህርት ቤት ለማገዝ ያለን የጋራ ስሜት ይሄንን ስራ እንድንሰራ አነሳስቶናል። ዋና ትኩረታችን ተማሪዎችንና ማህበረሰቡን ባለን ሞያ መርዳት ሲሆን ሌሎች ወንድም እህቶቻችን ይሄንን መነሻ በማድረግ ከኛ የተሻለ ነገር ለማህበረሰቡ እንዲሰሩ አርአያ መሆን ነው። እንደ ማጠቃለያ በዚህ ፋውንዴሽን መርህ መሰረት በግልፀኝነትና በትጋት አብረን በመስራት፣ ለሁሉም ማህበረሰብ ዘላቂ የሆኑ እድሎችን መፍጠር ዋና ተግባራችን ነው።